← All news
News Aug 24, 2026 · 14d ago

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ 125 ሚሊዮን ዶላር በጨረታ ሊሸጥ ነው

​የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ረቡዕ፣ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም  በሚያካሂደው  የ27ኛው ዙር የውጭ ሀገር ገንዘብ (FX) ጨረታ  ይፋ  አድርጓል። ​በዚህ ጨረታ ላይ 125 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ለጨረታ የሚቀርብ ሲሆን፣ ፍላጎት ያላቸው ባንኮች የተዘጋጀውን መመሪያ ተከተለው እንዲወዳደሩ ተጠይቀዋል። ​የጨረታ ሰዓት: ከጠዋቱ 4:00 እስከ ቀኑ 6:00 ሰዓት ​የማስገቢያ መንገድ: በCSD ኤሌክትሮኒክ የሐራጅ ሥርዓት በኢሜይል ​ውጤት የሚገለጽበት: በዕለቱ ከሰዓት በ9:00 ሰዓት ​ክፍያና ሂሳብ ማጣሪያ : ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም የሥራ ቀን ማጠቃለያ ላይ ይፈጸማል።