← All news
News Aug 23, 2026 · 16d ago

የገቢዎች ቢሮ በኮሚሽን ነጋዴዎች ግቢ የሚገኙ ተሽከርካሪዎች በአስቸኳይ እንዲነሱ አዘዘ

የገቢዎች ቢሮ በኮሚሽን ነጋዴዎች ግቢ የሚገኙ ተሽከርካሪዎች በአስቸኳይ እንዲነሱ አዘዘ የአዲስ አበበ ገቢዎች ቢሮ በተሽከርካሪ ኮሚሽንና አገናኝነት ስራ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች የሻጮችን ተሽከርካሪ በድርጅታቸው ቅጥር ግቢ አከማችተው መሸጥ በህግ የተከለከለ መሆኑን በመግለጽ፣ በግቢያቸው የሚገኙ መኪኖችን በአስቸኳይ እንዲያነሱ ጥብቅ ትእዛዝና ማስጠንቀቂያ አስተላልፏል። ቢሮዉ ያስተላለፈውን ጥብቅ መመሪያ ተከትሎ በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ አብዛኞቹ የኮሚሽን ነጋዴዎች ተሽከርካሪዎችን ከግቢያቸው እያወጡ ይገኛሉ።