← All news
News Jul 29, 2026 · 41d ago

ኢትዮጵያውያን ዜጎች ወደ ሩሲያ መግባት የሚያስችላቸው የኢ-ቪዛ አገልግሎት የሚያገኙበት አሠራር በቅርቡ ይፋ ሊደረግ ነው

ሩሲያ ለኢትዮጵያ፣ ለታንዛኒያ እና ለግብፅ ዜጎች የኢ-ቪዛ አገልግሎት መስጠት የምትችልበትን እድል በማጥናት ላይ እንደምትገኝ የሩሲያ የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ለሀገሪቱ መገናኛ ብዙኃን አስታውቋል።   ሚኒስቴሩ አክለሎም፣ "የኢ-ቪዛ ማመልከቻ እድልን ለኢትዮጵያ፣ ታንዛኒያ እና ግብፅ ለማስፋፋት እንዲሁም ለበርካታ ጊዜ መግባት የሚያስችለውን የኢ-ቪዛ አማራጭን ለማስተዋወቅ ከሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር እየሠራን ነው" ብሏል ሲል ስፑትኒክ ዘግቧል።