የተከለከሉ ፕላስቲኮችን ሲያከፋፍሉ የተገኙ 46 የምርት አከፋፋዮች መዘጋታቸውን የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን አስታወቀ
ይህ የተገለጸው ባለሥልጣኑ በትናንትናው ዕለት ባስጀመረው 3ኛ ዙር “ፅዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ” የከተማ አቀፍ መድረክ ላይ ነው። በፕላስቲክ ብክለት ቁጥጥር ሥራ 150 ልዩ ልዩ አካላት ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ የቅጣት ገንዘብ እንደከፈሉ በመድረኩ ተገልጿል። ኢትዮጵያ ለአንድ ጊዜ አገልግሎት የሚውሉ የፕላስቲክ ምርቶችን የሚከለክል መመሪያ ከጥር 23፣ 2018 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ሚድረጓ የሚታወቅ ነው።